ከላይ በርዕሱ እንደተገለጸዉ በጽዳት ዘመቻዉ መምህራን፤ ተማሪዎች እንዲሁም የአስተዳደር ሰራተኞች የተሳተፉ ሲሆን፤ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ይህንን የበጎ
አድራጎት ስራ ለመስራት ዩኒቨርሲቲዉ የሰጠዉን አቅጣጫ ተከትሎ ሃላፊነት በመዉሰድ ያስተባበረ መሆኑን የዩኒቨርሲቲዉ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፐሬዝደንት ገልጸዋል፡፡ እንደ ም/ፐሬዝደንትቱ ገለጻ ይህም የበጎ አድራጎት ስራ ቀጣይነት እንደሚኖረዉ ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የዩኒቨርሲቲዉ ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተርም ይህ የበጎ አድራጎት ስራ ዩኒቨርሲቲዉንና ማህበረስቡን የማስተሳሰር አቅም እንዳለዉ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም አንዳንድ ተማሪዎች፤ መምህራን፤ እንዲሁም የአካባቢዉ ነዋሪዎች የዩኒቨርሲቲዉ ማህበረሰብ በኔነት ስሜት ይህን በጎ ተግባር በማከናወኑ መደሰታቸዉን ገልጸዋል፡፡